የሴቶች መብት
ስራን መስራት የማንኛዉም ሰዉ ግዴታ ነዉ፡፡ ምክንያቱም አንድ ሰዉ ስራ ካልሰራ መኖር ስለማይችል ነዉ፡፡ በአሁኑ ሠዓት የሴትና የወንድ ብለን የምንለየዉ የስራ አይነት ባይኖርም እያንዳንዱ ሰዉ ግን መስራት የሚችለዉን ነገር መስራት እንዳለበት ሁላችንም ማወቅ ይኖርብናል፡፡ በገጠራማዉ የሀገራችን ክፍል ባለዉ አናሳ አስተሳሰብ ሴቶች እና ህጻናት ከጉልበታቸዉ በላይ የሆነ ሥራን ሲሰሩ እንመለከታለን፡፡ የሴቶች መብት በማይከበርበትና እምብዛም በማይታወቅበት የሀገራችን ገጠራማዉ ክፍል ብዙዉን ጊዜ የሴቶችን ጥቃት እንመለከታለን፡፡ ሴቶች ይጠለፋሉ፣ይደፈራሉ፣ከአቅማቸዉ በላይ የሆነን ስራ ይሰራሉ፣በቤተሰብ አማካኝነትም ለማያዉቁት ሰዉ ይዳራሉ፡፡ ይህን በመሰለዉ የሀገራችን ክፍል እንዴት አድርገን የሴቶችን ጥቃት ልናስቆም እንደምንችል ባይታወቅም እያንዳንዱ የሀገራችን ማህበረሰብ ግን ሴቶችን ከጥቃት ማዳን እንዳለበት ማሳሰብ እወዳለሁ፡፡ ሴቶች መሥራት ይችላሉ ፣እራሳቸዉን ማስተዳደር እና ሀላፊነታቸዉንም መወጣት ይችላሉ አመሰግንለሁ












Post new comment